ቀን 11/6/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ለቢሮው ሰራተኞች በመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 56/2010 ዙሪያ  ስልጠና መስጠት መጀመሩን አስታወቀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ ጋር በመተባበር ለቢሮው ሰራተኞች ስልጠና መስጠት መጀመሩን ያሳወቀ ሲሆን  ስልጠናው በዋናነት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወጣው የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 56/2010 ዙሪያ ሰራተኞች በቂ ግንዛቤ ይዘው እና መብትና ግዴታቸውን አውቀው ስራቸውን በአግባቡ መስራት እንዲችሉ ታስቦ መዘጋጀቱን የቢሮው የሰው ሀብትአስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ብዙነህ በቀለ ገልጸው አዋጁ በዋናነት ስለ ከባድና ቀላል የዲሲፒሊን ቅጣቶች፤ የአመት እረፍት አሰጣጥና ያለ ደሞዝ እረፍት አወጣጥን የተመለከቱ እና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮችን እንዳካተተ አስረድተዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ እንዳለ በስልጠናው መክፈቻ ባስተላለፉት መልዕክት ሰራተኛው አዋጆችን እና መመሪያዎችን በአግባቡ ተገንዝቦ ስራውን መስራት ከቻለ ውጤታማ መሆን እንደሚችል ጠቁመው በዚህ ስልጠናም ተሳታፊ የሆኑ ባለሙያዎች እስካሁን ያከናወኑዋቸው ተግባራት ከመመሪያና ደንብ አንጻር ምን እንደሚመስሉ እንዲሁም በቀጣይ ጊዜያትም ስራቸውን እነዚህኑ መመሪያዎች እና አዋጆችን ተከትለው መስራት እንዲችሉ እነደሚረዳቸውም አስታውቀዋል ፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s