ቀን 16/5/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ፆታዊ ጥቃትን መሰረት ያደረገ ስልጠና ሰጠ፡፡

በስልጠናው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የስርአተ ፆታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ አበባ ዘውዴ እንዳሉት ትምህርት ቤቶች ከመማር ማስተማር ጎን ለጎን በትምህርት ቤት ማሻሻል መርሃ ግብርና በራስ አቅም ጾታን መሰረት ያደረገ ጥቃትን ለመከላከል የተሻለ አፈፃፀም ያላቸውን ት/ቤቶች ልምድ ለሌሎች በማሳየት ልምድ ለመስጠት እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡

ፆታዊ ጥቃትን ለመከላከል በሁሉም ክፍለ ከተሞች እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን በተመለከተ የተሰበሰበ ቼክ ሊስት ውጤት እንደሚያሳየው አሁንም በበቂ ሁኔታ የወንዶችና ሴቶች መፀዳጃ አለመለየትና ምቹ አለማድረግ እንዲሁም የሴቶች የንፅህና መጠበቂያና በወር አበባ ጊዜ እረፍት ለሚፈልጉ ተማሪዎች የተዘጋጀ ማረፊያ አለመኖርና የመሳሰሉ ችግሮች እንደሚታዩ የገለፁት የሥርአተ ፆታ ባለሙያዋ ወ/ሮ ትእግስት በሪሁን በስልጠናው የሚሳተፉ የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው ክበባት ሀላፊዎች በክትትልና ድጋፍ የታዩ ክፍተቶችን ለመሸፈንና ዝቅተኛ አፈፃፀም ያሳዩ ትምህርት ቤቶችን ለማብቃት እድል እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል፡፡

ስልጠናዉ ፆታዊ ጥቃትን ከመከላከል ረገድ ዝቅተኛ አፈጻፀም የታየባቸው ት/ቤቶችን ለመደገፍ የተሻለ አፈፃፀም ያላቸውን ት/ቤቶች የአሰራር ዘዴዎች መውሰድ የበለጠ አቅም እንደሚፈጥር ተገልፃል፡፡

ስልጠናው ጥቃትን ከመከላከል አንፃር በ11 ዱ ክፍለ ከተሞች የተሻለ አፈፃፀም ላሳዩ የክ/ከተማና ወረዳ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ባለሞያዎች፤ ሱፐር ቫይዘሮችና ርዕሳነ መምህራን በሶስት ዙር እንደሚሰጥ ከዳይሬክቶሬቱ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s