ቀን 10/5/2014 ዓ.ም
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የወሳኝ ኩነት ጽ/ቤት የተማሪዎች የልደት ካርድ ምዝገባ ማከናወን ጀመረ፡፡
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ቅ/ጽ/ቤት ከትምህርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ፕሮግራም “የተማሪ የልደት ምዝገባ ለተሻለ የትምህርት ጥራት” በሚል መሪ ቃል በጎሮ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት የከተማ፣የክ/ከተማና የወረዳ አመራሮቾን ፣ መምህራንና ተማሪዎችን ያሳተፈ የተማሪዎች የልደት ካርድ ምዝገባ ንቅናቄ ማድረክ አካሂዳል፡፡
በእለቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ታከለ ነጫና ፣የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳዊት ወልደየሱስ እና የወሳኝ ኩነት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ባጫ ጅረኛ በስፍራው ተገኝተዋል፡፡
በንቅናቄው ፕሮግራም ላይ የተገኙት ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚው የመክፈቻ ንግግር በማድረግ የልደት ምዝገባ ንቅናቄውን በይፋ አስጀምረዋል።
የለሚ ኩራ ወሳኝ ኩነት ሀላፊም በበኩላቸው የልደት ካርድን ከወሳኝ ኩነት ጽ/ቤት መውሰድ ያለውን ጠቀሜታ እና ሌሎች ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች በተመለከተ አጭር ማብራሪያ መስጠታቸዉን ከክፍለ ከተማዉ ት/ጽ/ቤት እና ኮሚዩኒኬሽን ያገኘነዉ መረጃ ያሳያል፡፡
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ…
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: – aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/
ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

