ቀን 20/4/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ቡድን በቅርቡ በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለተመደቡ የአይ ሲ ቲ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ።

ስልጠናው በዋናነት በስኩል ኔት መሰረት ልማት አጠቃቀም እና ተዛማጅ ጉዳዮችን በተመለከተ የተዘጋጀ ሲሆን ስልጠናውም በስራ ክፍሉ ባለሙያዎች በአቶ ታዬ ወልደኪዳን እና በአቶ ሚካኤል መስፍን ነው የተሰጠው።

በስልጠናው መክፈቻ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ እንዳስታወቁት ስልጠናው በቅርቡ ቢሮው ባወጣው ማስታወቂያ ተወዳድረው በየትምህርት ቤቱ የተመደቡ ባለሙያዎች ሙያዊ ክህሎታቸውን ማሻሻል እንዲችሉ ታስቦ መዘጋጀቱን ገልጸው የስልጠናው ተሳታፊዎችም በትምህርት ቤቶች ያሉ የአይ ሲ ቲ መሰረተ ልማቶች ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የስልጠናው ተሳታፊዎች በቀረቡ የስልጠና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ አስተያየቶችን እና ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን በዋናነትም የስራ ድርሻቸው በአስቸኳይ ለትምህርት ቤቶች ቢላክ የሚልና አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ተገቢውን ድጋፍ አለማድረጋቸውን አንስተው በቢሮው የአጠቃላይ ትምህርት ቴክኖሎጂ ልማትና ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በሆኑት በአቶ በለጠ ንጉሴ እና በኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ቡድን መሪው በአቶ ደረጀ ዳኜ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቷል።

አካባቢያችንን #እንጠብቅ

ወደ ግንባር #እንዝመት

መከላከያን #እንደግፍ

ከደጀን እስከ ግንባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ነን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s