የ’በቃ’ ‘#NoMore’ ዘመቻ በአውስትራሊያ ሜልቦርን ከተማ በአውስትራሊያ ፓርላማ ፊት ለፊት ተካሄደ።
ሰልፈኞቹ ባሰሙት መፈክር የምዕራቡ ዓለም አንዳንድ አገራት በኢትዮጵያ ላይ እያደረጉት ያለውን ያልተገባ ጫናና ጣልቃ ገብነት አውግዘዋል።
የምዕራባውያኑ መገናኛ ብዙሃኖች በኢትዮጵያ ላይ የሚያሰራጯቸውን ሀሰተኛ ዘገባዎችን እንዲያቆሙና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አሸባሪው ሕወሓት በአማራና አፋር ክልሎች የፈጸማቸውን በደሎች እንዲያወግዙ ጠይቀዋል።
አሸባሪው የሕወሓት ቡድን ድርጊቶች በዓለም አቀፍ ወንጀል የሚያስጠይቅ እንደሆም አስገንዝበዋል።
‘ኢትዮጵያ አትፈርስም፣ ኢትዮጵያ ታሸንፋለች፣ ከኢትዮጵያ ሕዝብና መንግስት ጎን ነን፣ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በሕዝብ ድምጽ የተመረጠውን መንግስት ማክበርና እውቅና መስጠት አለበት’ የሚሉና ሌሎች ‘የበቃ’ እንቅስቃሴ መልዕክቶች በሰልፉ ላይ ተላልፈዋል።
‘የበቃ’ ወይም ‘#NoMore’ ዘመቻ አካል የሆኑ ሰላማዊ ሰልፎች ዛሬ በዴንማርክ ኮፐንሀገንና በግሪክ አቴንስ ይካሄዳሉ።
‘የበቃ’ ወይም #NoMore እንቅስቃሴ አፍሪካ፣ አውሮፓ፣ እስያ፣ ሰሜን አሜሪካና ኦሺኒያ አህጉራትን አዳርሷል።
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
ሠራዊቱን ይደግፉ!
ከደጀን እስከ ግንባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ነን!
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: – aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/
ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!
