ቀን 23/3/2014 ዓ.ም

ባገኘነው ድል ሳንዘናጋ ለአፍታም አይንና ጆሮአችንን ከአካባቢያችን ሰላምና ፀጥታ ላይ ማንሳት የለብንም ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ::

በምስራቅ የጀመረው ድል በአጭር ጊዜ ጋሸናና ሸዋ ደርሷል ያሉት ከንቲባ አዳነች በታሪካዊው ድል ከፍተኛ የአመራር ሰጪነት እና የአገር ፍቅርን በተግባር ለገለፁት ለኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና ለጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶ/ር ዐብይ አህመድ  እንዲሁም ለከፍተኛ የጦር አመራሮች፤ ጀግናው የኢፌዴሪ  የመከላከያ ሰራዊትና የፀጥታ ሀይሎች ያላቸዉን ወደር የማይገኝለት አክብሮትና አድናቆት ገልፀዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ መላው ህዝባችን ለተገኘው አንጸባራቂ ድል እንኳን ደስ አለን በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

“መላው የከተማችን ነዋሪዎች ፣ የፀጥታ ሀይሎች እና አመራሮች ባገኘነው ድል ሳንዘናጋ ትኩረታችን የከተማችን ፀጥታ ላይ እናድርግ ሲሉ አሳስበዋል፡፡

አሸባሪው የህወሃት ጁንታ ቡድን  በየሄደበት የፈሪ የጥፋት በትሩን በንጹሃን ዜጎች እና ንብረት ላይ  የሚያደርስ ቡድን እስከወዲያኛው ወደ መረጠዉ ሲኦል እስኪሸኝ ለአፍታም አይንና ጆሮአችን ከአካባቢያችን  ሰላምና ፀጥታ ላይ ማንሳት የለብንም”  ብለዋል፡፡

“አሁንም ፀጉረ ልውጦችና ሰርጎ ገቦችን እንዲሁም በህገ ወጥ ያከማቹትን የጦር መሳሪያ እየተከታተልን ለህግ እናቅርብ” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

አካባቢዎን ይጠብቁ!

ወደ ግንባር ይዝመቱ!

ሠራዊቱን ይደግፉ!

ከደጀን እስከ ግንባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ነን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s