ቀን 8 / 4 / 2013 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ4ኛ ዙር ከፊታችን ሰኞ ከታህሳስ 12/4/2013 ዓ/ም ጀምሮ ወደ ገጽ ለገጽ የመማር ማስተማር ስራ የሚገቡ የክፍል ደረጃዎችን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ይፋ አደረገ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ ደሙ በዛሬዉ እለት በሰጡት መግለጫ እንዳሳወቁት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን እየተከላከሉ የገጽ ለገጽ የመማር ማስተማር ስራዉን በከተማዉ ለማስጀመር በተቀመጠዉ ውሳኔ መሰረት ቀደም ሲል ህዳር 16 የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎቸ በክለሳ ትምህርት ውስጥ እንዳልፉ ፣  ህዳር 28 በግል ትምህርት ቤቶች ከ1 ክፍል ጀምሮ እና በመንግሰት ትምህርት ቤቶች ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ በሶስት ዙሮች መጀመሩን ገልጸዉ ከፊታችን ሰኞ ከታህሳስ 12/4/2013 ዓ/ም ጀምሮ በ4ኛ ዙር ወደ ገጽ ለገጽ የመማር ማስተማር ስራ የሚገቡ የክፍል ደረጃዎች በግል ትምህርት ቤቶች የቅድመ መጀመሪያ ደረጃ ተማሪዎች እና በመንግስት ትምህርት ቤቶች ከ1ኛ – 4ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች መሆናቸዉን ሀላፊዉ አሳውቀዋል፡፡

ሀላፊዉ በመግለጫቸዉ አክለዉም ህጻናት ተማሪዎችን ወደ ገጽ ለገጽ የመማር ማስተማሩ ስራ እያመጣን በመሆኑ የተዘጋጀዉን የኮቪድ ፕሮቶኮልን በአግባቡ መተግበር እንዲቻል የትምህርት ባለድርሻ አካላት የበኩላቸዉን ሚና እንዲወጡ ጥራቸዉን አቅርበዋል፡፡  

መረጃዎችን  በፍጥነት  ለማግኘት የዩቲዩብ ፣ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ እና  የትዊተር  ገፃችንን  ሰብስክራይብ  ያድርጉ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

ባልታጠበ  እጅ  አይንዎን  አፍዎን  እና  አፍንጫዎን  ባለመንካት  በዙሪያዎ  ላሉ  ሰዎች  አርአያ  ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s