ቀን 15 / 09 / 2012 ዓ/ም

እናመሰግናለን ! አብዝቶ ይስጥልን !

 ት/ቤቶች ማህበራዊ  ኃላፊነታቸዉን ከመወጣት አንፃር አርአያነት ያለው ተግባር እየሰሩ ይገኛሉ፡፡

በንፍስ ስልክ ላፍቶ ክፈለ ከተማ  አባይ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የሚገኙ  መምህራንና የአስተዳደር  ሰራተኞች ለ 65 በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ የተማሪ ወላጆች በጥሬ ገንዘብ ፣ የምግብና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ  ድጋፍ አድርገዋል።

በድጋፉ ወቅት የተገኙት የክፍለ ከተማችን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ካሳሁን የትምህርት ተቋማትና ሰራተኞች  እያደረጉት ያለው መልካም ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል። አቶ ፍቃዱ አክለውም የመጣብንን የተፈጥሮ አደጋ ለመከላከል ሁሉም በያለበት ሊረባረብ ይገባል ። ይህ ክፉ ቀን ያልፋል ሁላችንም ካለን እናካፍል መምህራን የሁላችንም አርያ ናችሁ በርቱ እንበረታለን ሲሉ በአስተዳደሩ ስም ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል ።

በዚሁ ከፍለ ከተማ  በወረዳ 05 እና 02 አስተዳደር ስር የሚገኙት  ዴስትኒ አካዳሚ እና የኔታ አካዳሚ ገቢያቸው አነስተኛ ተብለው ለተለዩ 180  አባወራዎችና እማወራዎች ከ 180 ሺ ብር በላይ ወጪ በማድረግ የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችንና የተለያዪ ምግቦችን የክፍለ ከተማና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ድጋፍ አድርገዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ለማግኘት የዩቲዩብ ፣ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ እና የትዊተር ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

 Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Facebook : https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication እንራራቅ፣ እንታጠብ እንዲሁም አንጨባበጥ፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s