መግቢያ

አገራችን በነደፈችው የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ህዝባችንን ከድህነትና ኋላ ቀርነት ለማላቀቅ በትምህርትና ስልጠና ለመለወጥ ሁሉም ዜጎች የትምህርት እድል ተጠቃሚ መሆን አለባቸው መንግስትም የዜጎችን አቅም በትምህርት ስልጠና የማጎልበትን አስፈላጊነት በጽኑ አምኖ በወሰዳቸው እርምጃዎች በጥቂቱ ዐመታት ከፍተኛ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ የትምህርት አቅርቦትን በማስፋፋት ብዙ የተጓዝን ቢሆንም አሁንም የትምህርት ዕድል ያላገኙ ዜጎች መኖራቸው እሙን ነው፡፡ከቦታ ቦታ ያለውን ያለመመጣጠን በሴቶችና በወንዶች መካከል ያለውን የተሳትፎ ልዩነት ለማጠበብ ቀላል የማይባሉ ተግባሮች ተከናውነዋል፡፡

ራዕይ

በአዲስ አበባ ከተማ ውጤታማ የትምርት ሥርአት መማስፈን በ 2012 እ.ኤ.አ ዓለም ዓቀፋው ተወዳዳር የሆኑ የትምህርት ተቋማት በልማት በዲሞክራሲና መልካም አስተዳደር ግንባታ ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ስብዕና ያላቸው ዜጎች ማፍራት፡፡

ተልዕኮ

የአዲስ አበባ ከተማን ነዋሪ በትምህርት ስራ ላይ በባለቤትነት በማሳተፍ ለትምህርት መዋቅሩ አካላትላ በትምህርት መስክ ለተሰማሩ ባለሃብቶች ሙያዊና ቴክኒካዊ ድጋፍ በመስጠት፡አጋር ድርጅቶችን በማስተባበር የትምህርት ተቋማትን በፍትሐዊነት በማስፋፋት የከተማዋን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ አለምአቀፋዊ ደረጃውን የጠበቀና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ትምህርት በተስማሚ ፕሮግራሞች ለህብረተሰቡ ማድረስ፡፡

እሴቶች

  • ለትምህርት ጥራት ቅድሚያ እንሰጣለን
  • በመልካም ሥነምግባር የታነጹ ዜጎችን እንፈጥራለን
  • ፈጠራና ችግር ፈቺነት አናበረታታለን
  • በጥናትና ምርምር የትምህርት ችግሮቻችን እንፈታለን
  • በእውቀትና በ እምነት እንሰራለን
  • ግልጽነት
  • ተጠያቂነት
  • ለለውጥ ዝግጁ ነን
  • የላቀ አገልግሎት እንሰጣለን
  • በጋራ መስራት

Leave a comment